ከፍተኛ ውኃ የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ከውኃ እጥረት ጋር በተያያዘ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ችግሮችን ለመከላከልና በዘርፉ በጋራ ለመሥራት ጥምረት በይፋ መሠረቱ፡፡
ጥምረቱን የመሠረቱት ከፍተኛ ውኃ የሚጠቀሙት የታሸገ ውኃ፣ የለስላሳ መጠጥ፣ የጭማቂ፣ የቢራና የሌሎች የአልኮል መጠጥ ፋብሪካዎች ናቸው፡፡
ሐሙስ ነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በይፋ የተመሠረተው ጥምረት፣ በውኃና ወኃ ነክ ምርት ላይ የተሰማሩ ፋብሪካዎች የፋብሪካዎቹ ዋና ጥሬ የሆነውን ውኃ በአግባቡ የመጠቀም አስፈላጊነት ላይ በመግባባት ለዚሁ ጉዳይ የሚሠራ ጥምረት አቋቁመዋል፡፡