የታሸገ ውኃ አምራቾች በዓመት ወጪ ያደርጉ የነበረው 100 ሚሊዮን ዶላርን የሚያስቀር ማስተርባች የተሰኘ ምርት መጠቀም እንዲያቆሙ መወሰኑን የኢትዮጵያ ውኃ፣ ለስላሳ መጠጦች፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች ማኅበር ገለጸ።
የታሸገ ውኃ አምራቾች በተለይም በጥሬ ዕቃ እጥረት ለማምረት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና ለዚህም እንደ መፍትሔ ከተወሰዱት ጉዳዮች መካከል ተጨማሪ ግብዓቶችን መጠቀም ማቆም መሆኑን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አሸናፊ መርዕድ ገልጸዋል።